ወደ ዋናው ገፅ ለመሄድ

የአሠራር ዘዴያችን

© Welthungerhilfe
© Welthungerhilfe

ረሀብ በዓለም ላይ እጅግ በጣም የገዘፈ ችግር ነው፡፡ ሆኖም ሊፈታ የሚችል ችግር ነው፡፡ የቬልትሁንገርሂልፌ (Welthungerhilfe) ራዕይ እያንዳንዱ ሰው ሰብአዊ ክብር ኖሮት፣ ከረሀብና ከድህነት ነፃ  ሆኖ በራሱ የሚመራበትን ሕይወት የሚኖርበትን ማየት ነው፡፡

የቬልትሁንገርሂልፌ እስትራቴጃዊ ግብ በተባበሩት መንግስታት ሁለተኛው ዘላቂ ልማት ግብ ላይ ተመስርቶ እኛ በምንሠራባቸው አካባቢዎች ሁሉ እስከ 2030 (እኤአ) ረሀብን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ ነው፡፡   እኛ በንቃት በምንቀሳቀስባቸው አገሮች ሁሉ ከአካባቢው ተባባሪ አካላት ጋር በመሥራት ረሀብን ለማጥፋት እንፈልጋለን፡፡ የሥራ እንቅስቃሴዎቻችን የዛሬና የወደፊት ትውልዶች ጤናማ አካባቢና የሚተሳሰብ ማህበረሰብ እንዲኖራቸው በመርዳት ዕጣ ፈንታቸውን ማሻሻልን ታሳቢ ያደረጉ ናቸው፡፡

ረሀብን የማጥፋት የአሠራር ዘዴ

በዓለምአቀፍ ደረጃ ረሀብን ለማጥፋትና ለዘለቄታዊ የምግብ ዋስትና እንታገላለን፡፡ ይህም ትግላችን ጤናን፣ ትምህርትንና የኢኮኖሚ ልማትን ከማሻሻል ጎን ለጎን በተወሰነ አካባቢ ላይ የሚከናወን ግብርናን፣ የንፁህ ውሃና ለተፈጥሮ አካባቢ የሚስማማ ንፁህ ኢነርጂ አቅርቦትን ያካትታል፡፡

© Welthungerhilfe
© Welthungerhilfe

 ራስን በራስ ለመምራት መጣጣር

ዓላማችን የሕዝቦችን ሕይወት በረጅም ጊዜ ሂደት ማሻሻል ነው፡፡ በመሆኑም‘ራሱን እንዲረዳ እርዳው’ በሚለው መርህ ላይ ተመስርተን እንሠራለን፡፡ ፕሮግራሞቻችን ሰዎች የራሳቸውን ሕይወት ራሳቸው እንዲመሩና ምግብ የማግኘት ሰብአዊ መብታቸውን ለማረጋገጥ እንዲችሉ ተደርገው የተቀረጹ ናቸው፡፡

የቬልትሁንገርሂልፌ የአሠራር ዘዴዎች በአንድ የተወሰነ የፕሮጄክት ሥራ እንቅስቃሴዎችና የፖለቲካ አስተምህሮ ሥራ ላይ የተመሰረተ አይደለም፡፡ ይልቁንም ሊመዘኑ የሚችሉ ውጤቶችና ለባለድርሻ አካላት፣ ለለጋሾችና በፕሮጄክቱ አካባቢ ለሚገኘው ሕዝብ ተጠያቂ መሆን ላይ የሚመሰረት ነው፡፡

በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የረሀብ ማብቂያውን አሁን እየደረስንበት ነው፡፡ እንደበርካታዎቹ በልማት ትብብር ሥራዎች ላይ የተተሳተፉ ብዙ ወገኖች ሁሉ ወደ ፊት በአንድ ወቅት ላይ ሥራችን አስፈላጊነቱ እንደሚያበቃ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ይህን ራዕያችንን እንድንቀዳጅ አግዙን፤ ከረሀብ ነፃ ለሆነች ዓለም በምናደርገው ትግል  ተሳተፉ፡፡